ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ እና ድህረ ምረቃ #የክረምት መርሃ ግብር #ነባር ተማሪዎች ምዝገባ ሐምሌ 23 እና 24/2013 ዓ.ም እንደሆነ ገልጿል።
የቅድመ እና ድህረ ምረቃ #የክረምት #አዲስ ገቢ ተማሪዎች ምዝገባ ሐምሌ 26 እና 27/2013 ዓ.ም መሆኑንም አሳውቋል።
ከአንደኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች ጥሪ ጋር በተያያዘ የግቢ ውስጥ አገልግሎት እጥረት እንዳጋጠመው የገለፀው ዩኒቨርሲቲው፤ በዚህ ዓመት በመንግስት ስፖንሰር ለተደረጉ የክረምት ተማሪዎች ብቻ የምግብ እና የዶርም አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል፡፡
በተገለፁት ቀናት ብቻ የሚመጡ የክረምት ተማሪዎችን እንደሚያስተናግድ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል። #ደማዩ